104 · Makkī

الهمزة

Al-Humaza·The Traducer

✦ memorize this sūrah

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

  1. وَيْلٌ لِّكُلِّ هُمَزَةٍ لُّمَزَةٍ﴿١﴾

    ለሃሜተኛ ለዘላፊ ሁሉ ወዮለት፡፡

  2. ٱلَّذِى جَمَعَ مَالًا وَعَدَّدَهُۥ﴿٢﴾

    ለዚያ ገንዘብን የሰበሰበና የቆጣጠረው (ያደለበውም) ለኾነ ፤(ወዮለት)፡፡

  3. يَحْسَبُ أَنَّ مَالَهُۥٓ أَخْلَدَهُۥ﴿٣﴾

    ገንዘቡ የሚያዘወትረው መኾኑን ያስባል፡፡

  4. كَلَّا لَيُنۢبَذَنَّ فِى ٱلْحُطَمَةِ﴿٤﴾

    ይከልከል፤ በሰባሪይቱ (እሳት) ውስጥ በእርግጥ ይጣላል፡፡

  5. وَمَآ أَدْرَىٰكَ مَا ٱلْحُطَمَةُ﴿٥﴾

    ሰባሪይቱም ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?

  6. نَارُ ٱللَّهِ ٱلْمُوقَدَةُ﴿٦﴾

    የተነደደችው የአላህ እሳት ናት፡፡

  7. ٱلَّتِى تَطَّلِعُ عَلَى ٱلْأَفْـِٔدَةِ﴿٧﴾

    ያቺ በልቦች ላይ የምትዘልቅ የኾነችው፡፡

  8. إِنَّهَا عَلَيْهِم مُّؤْصَدَةٌ﴿٨﴾

    እርሷ በእርግጥ በእነርሱ ላይ የተዘጋጀች ናት፡፡

  9. فِى عَمَدٍ مُّمَدَّدَةٍۭ﴿٩﴾

    በተዘረጋች አዕማድ ውስጥ (የተዘጋች ናት)፡፡

Quran Translation Name: ሳዲቅ & ሳኒ ሐቢብ Translator: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib Language: Amharic ID: am.sadiq Last Update: August 3, 2012 Source: Tanzil.net

Play surah