99 · Madanī

الزلزلة

Az-Zalzala·The Earthquake

✦ memorize this sūrah

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

  1. إِذَا زُلْزِلَتِ ٱلْأَرْضُ زِلْزَالَهَا﴿١﴾

    ምድር (በኀይል) መንቀጥቀጥዋን በተንቀጠቀጠች ጊዜ፤

  2. وَأَخْرَجَتِ ٱلْأَرْضُ أَثْقَالَهَا﴿٢﴾

    ምድር ሸክሞችዋን ባወጣችም ጊዜ፤

  3. وَقَالَ ٱلْإِنسَٰنُ مَا لَهَا﴿٣﴾

    ሰውም ምን ኾነች? ባለ ጊዜ፤

  4. يَوْمَئِذٍ تُحَدِّثُ أَخْبَارَهَا﴿٤﴾

    በዚያ ቀን ወሬዎችዋን ትናገራለች፡፡

  5. بِأَنَّ رَبَّكَ أَوْحَىٰ لَهَا﴿٥﴾

    ጌታህ ለእርሷ በማሳወቁ ምክንያት፡፡

  6. يَوْمَئِذٍ يَصْدُرُ ٱلنَّاسُ أَشْتَاتًا لِّيُرَوْا۟ أَعْمَٰلَهُمْ﴿٦﴾

    በዚያ ቀን ሰዎች ሥራዎቻቸውን (ምንዳዋን) እንዲያዩ ይደረጉ ዘንድ (እንደየሥራቸው) የተለያዩ ኾነው (ከመቆሚያው ስፍራ) ይመለሳሉ፡፡

  7. فَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ خَيْرًا يَرَهُۥ﴿٧﴾

    የብናኝ ክብደት ያክልም መልካምን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

  8. وَمَن يَعْمَلْ مِثْقَالَ ذَرَّةٍ شَرًّا يَرَهُۥ﴿٨﴾

    የብናኝ ክብደት ያክልም ክፉን የሠራ ሰው ያገኘዋል፡፡

Quran Translation Name: ሳዲቅ & ሳኒ ሐቢብ Translator: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib Language: Amharic ID: am.sadiq Last Update: August 3, 2012 Source: Tanzil.net

Play surah