96 · Makkī

العلق

Al-Alaq·The Clot

✦ memorize this sūrah

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

  1. ٱقْرَأْ بِٱسْمِ رَبِّكَ ٱلَّذِى خَلَقَ﴿١﴾

    አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡

  2. خَلَقَ ٱلْإِنسَٰنَ مِنْ عَلَقٍ﴿٢﴾

    ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡

  3. ٱقْرَأْ وَرَبُّكَ ٱلْأَكْرَمُ﴿٣﴾

    አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤

  4. ٱلَّذِى عَلَّمَ بِٱلْقَلَمِ﴿٤﴾

    ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡

  5. عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ﴿٥﴾

    ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡

  6. كَلَّآ إِنَّ ٱلْإِنسَٰنَ لَيَطْغَىٰٓ﴿٦﴾

    በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡

  7. أَن رَّءَاهُ ٱسْتَغْنَىٰٓ﴿٧﴾

    ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡

  8. إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجْعَىٰٓ﴿٨﴾

    መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

  9. أَرَءَيْتَ ٱلَّذِى يَنْهَىٰ﴿٩﴾

    አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡

  10. عَبْدًا إِذَا صَلَّىٰٓ﴿١٠﴾

    ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤

  11. أَرَءَيْتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلْهُدَىٰٓ﴿١١﴾

    አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤

  12. أَوْ أَمَرَ بِٱلتَّقْوَىٰٓ﴿١٢﴾

    ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤

  13. أَرَءَيْتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ﴿١٣﴾

    አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤

  14. أَلَمْ يَعْلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ﴿١٤﴾

    አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?

  15. كَلَّا لَئِن لَّمْ يَنتَهِ لَنَسْفَعًۢا بِٱلنَّاصِيَةِ﴿١٥﴾

    ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡

  16. نَاصِيَةٍ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٍ﴿١٦﴾

    ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡

  17. فَلْيَدْعُ نَادِيَهُۥ﴿١٧﴾

    ሸንጎውንም ይጥራ፡፡

  18. سَنَدْعُ ٱلزَّبَانِيَةَ﴿١٨﴾

    (እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡

  19. كَلَّا لَا تُطِعْهُ وَٱسْجُدْ وَٱقْتَرِب﴿١٩﴾

    ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡

Quran Translation Name: ሳዲቅ & ሳኒ ሐቢብ Translator: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib Language: Amharic ID: am.sadiq Last Update: August 3, 2012 Source: Tanzil.net

Play surah