92 · Makkī

الليل

Al-Lail·The Night

✦ memorize this sūrah

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ

  1. وَٱلَّيْلِ إِذَا يَغْشَىٰ﴿١﴾

    በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

  2. وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ﴿٢﴾

    በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

  3. وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلْأُنثَىٰٓ﴿٣﴾

    ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

  4. إِنَّ سَعْيَكُمْ لَشَتَّىٰ﴿٤﴾

    ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

  5. فَأَمَّا مَنْ أَعْطَىٰ وَٱتَّقَىٰ﴿٥﴾

    የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

  6. وَصَدَّقَ بِٱلْحُسْنَىٰ﴿٦﴾

    በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

  7. فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْيُسْرَىٰ﴿٧﴾

    ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

  8. وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسْتَغْنَىٰ﴿٨﴾

    የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

  9. وَكَذَّبَ بِٱلْحُسْنَىٰ﴿٩﴾

    በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

  10. فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلْعُسْرَىٰ﴿١٠﴾

    ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

  11. وَمَا يُغْنِى عَنْهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ﴿١١﴾

    በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

  12. إِنَّ عَلَيْنَا لَلْهُدَىٰ﴿١٢﴾

    ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

  13. وَإِنَّ لَنَا لَلْـَٔاخِرَةَ وَٱلْأُولَىٰ﴿١٣﴾

    መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

  14. فَأَنذَرْتُكُمْ نَارًا تَلَظَّىٰ﴿١٤﴾

    የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

  15. صفحة ٥٩٦
  16. لَا يَصْلَىٰهَآ إِلَّا ٱلْأَشْقَى﴿١٥﴾

    ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

  17. ٱلَّذِى كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ﴿١٦﴾

    ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

  18. وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلْأَتْقَى﴿١٧﴾

    አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

  19. ٱلَّذِى يُؤْتِى مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ﴿١٨﴾

    ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

  20. وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعْمَةٍ تُجْزَىٰٓ﴿١٩﴾

    ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

  21. إِلَّا ٱبْتِغَآءَ وَجْهِ رَبِّهِ ٱلْأَعْلَىٰ﴿٢٠﴾

    ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

  22. وَلَسَوْفَ يَرْضَىٰ﴿٢١﴾

    ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡

Quran Translation Name: ሳዲቅ & ሳኒ ሐቢብ Translator: Muhammed Sadiq and Muhammed Sani Habib Language: Amharic ID: am.sadiq Last Update: August 3, 2012 Source: Tanzil.net

Play surah